ForeverMissed
Large image
Dear friends, family and colleagues,

This memorial website was created in memory of our beloved father, Tadesse Gessesse. We will remember him forever. Thank you for your messages, calls and support in these difficult times. 
He has left a huge mark in all of our lives and he will forever be remembered and cherished.
His untimely death has shocked us all and we feel unprepared to deal with life without him. He was the best father anyone could ever ask for, not only to his kids but to all those who viewed him as such. His generosity, kindness and empathy have had a tremendous impact in our lives and we hope to  continue his legacy and make him proud.

Please join us on this website to celebrate his life by sharing stories, photos and anecdotes. You will find personnal stories and pictures from the family in the "Gallery" and "Stories" tabs.

Thank you for helping us celebrate him and grieve his untimely passing.

With love,
His family and loved-ones, 

*In order to contribute to this site you will have to enter an email and create a password. We apologize for this inconvenience.
January 15, 2023
January 15, 2023
በዛሬው ቀን የታዴን ሁለተኛ የሙት አመት በማክበር ወንድማችንን እንድናስታው ተሰብሰበናል ፣ አወን ሁለት አመት ሆነ ታዴ ከተለየን ፣ የዛሬ ስድስት ወር ገደማ ፣ አዲስ ፍሬ  ት/ትቤ በታዴ ስም የጽሃፍት ቤቱን ሲያመርቅ ያነበብኩትን አጭር ጽሁፍ ከዘመድ ወዳጆቹ ጋር በመቋደስ የታዴን በጎ ስራዎች ማስታወስ ደስታዬ ነው ፣
ዘሪሁን ተክሌ .፣ ጥር 7 ፣ 2015

በአዲስ ፍሬ አንደኛ ደረጃ ት/ቤት ታደሰ ገሰሰ መጽህፍት ቤት ምረቃ/ 8 ጁን 2022.

ወንድማችን ታደሰ ከተለየን ሰነበተ ፣ አመት ፣ አመት ተኩል አለፈው....አሁንም ለዘላለም እንደተለየን ልቀበለው አልቻልኩም ፣ አልፈለኩም ፣ አሁንም ቀበሌ 19 ፣ የቼዝ ገበታው ፊት፣ በአርምሞ ሲያስብ ይታየኛል ፣፣

ከታደሰ ምንም ጊዜ የማልረሳው እንድ ትልቅ ቁም ነገር አለ ፣ ከሚወዳቸው ጥቅሶች አንዱ “ ደግነት ለራስ ነው ” የሚለው ነው ፣ ከዚህ ጥቅስ ጋር አንድ የተለየ ታሪክ አለኝ ፣ ታደሰ በብዛት እና በአይነት የላቁ የፊልም ፣ የሙዚቃ፣ የመጽሃፍት ፣ የልዩ ልዩ መጣጥፎች እራሱ የጻፋቸው እና ከሌሎችም ደራስያን የሰበሰባቸው ሰፊ ኮሌክሽን እንዳለው ብዙ ሰው ያውቃል፣፣ በየጊዜው የተወሰኑ የፊልም አይነቶች፣ አንዳንድ ዘፈኖች ፣ ከጻፋቸው ጽሁፎች የወቅቱን ሁኒታ ያብራራሉ ብሎ የሚገምታችውን በሲዲ ፣ በሜሞሪ ስቲክ እየቀረጸ ይሰጠኛል ፣ እንድ ቀን እንደውም በሙሉ የሃርድ ዲስኬን እንዳለ ለምን አልገለብጥልህም፣ ከፍ ያለ የክምችት ካፓሲሲቲ ያለው ኤክስተርናል ዲስክ ይዘህ መጥተህ በሙሉ ያሉኝን ፋይሎች ልገልብጥልህ አለኝ ፣ እኔም በደስታ ተቀበልኩት ፣ ይሰነብትና የታደሰ ኮምፑተር ይሰረቃል ፣ ታደሰም ይደውልና “ደግነት ለራስ ነው ብዬህ የለ ፣ ኮምፑተሬ ተሰርቆ ሌላ ኮምፑተር ገዝቼአለሁ ፣ በል ፋይሎቼን መልስ “ አለኝ ፣፣ ከዚህ ያገኘሁት ትምህርት ፣ ደግነት ለአድራጊው ከሚሰጠው ደስታ እና ጸጋ ጋር አድራጎቱ ይዋል ይደር አንጂ ተመልሶ ለደግ አድራጊው ፣ ለባለቤቱ የሚመጣ መሆኑን ነው ፥፣ አሁንም አንድ ሰው ከመንገዱ ወጥቶ ለሌላው ሰው በጎ ነገር ሲሰራ ሳይ ፣ የታዴ ምስል ከፊቴ ድቅን ይላል ፣፣

ከሮታሪ ክለብ አዲስ አበባ እንጦጦ ወንድሞቹ እና እህቶቹ ጋር የአዲስ ፍሬ ት/ትቤን ለተማሪዎቹ ፣ ለመህራን፣ እንዲሁም ባጠቃላይ ለት/ቤቱ ማህረሰብ ምቹ ለማድረግ ታዴ ያላደረገው ጥረት የለም ፣ ለዚህም የአዲስ ፍሬ ማህበረሰብ ለታዴ ያለው አክብሮት እና ፍቅር ህያው ምስክር ነው፣፣ በተለይ ለትምህርት ጥራት ፣ ለእውቀት መዳበር የነበረው ጥጽኑ እምነት እና ጥረት የላቀ ነበር ፣ የት/ቤቱ መጻህፍት ቤት በወንድማችን በታደሰ ስም መሰየሙ ትክክል እና ተገቢ ነው ፣ ይህን በማድረግ መልካም ፈቃደኝነታቸውን እና ድጋፋቸውን ለሰጡን ለት/ቤቱ አመራር እና መምህራን ምስጋናችን ከፍ ያለ ነው፣ ይህ መጽሃፍት ቤት በት/ቤቱ ውስጥ ተገቢ ቦታውን ይዞ ‘’የእውቀት ማእከል’’ እንዲሆን የተቻለውን ጥረት ለማድረግ በሮታሪ ክለብ አዲስ አበባ እንጦጦ ስም ቃል እገባለሁ ፣፣

የታደሰን ነብስ በገነት ያኑርልን ፣፣

ዘሪሁን ተክሌ ፣ ሮታሪ ክለብ አዲስ አበባ እንጦጦ፣ የ2021/2022 ሊቀ መንበር
April 8, 2022
April 8, 2022
Nous étions dans la même classe de 1ère 1959-1960 et j'ai appris de ton décès en m'inscrivant à l'association des anciens élèves du Lycée Guebre Mariam d'Addis.
En 1958, mon père dirigeait la fabrique de coton à Dire-Dawa appartenant au Prince de Harar.
Nous nous sommes rencontrés à Dire-Dawa avec d'autres camarades de l'école dont Gaetano Trimarchi et Merzian.Nous sommes nés la même année 1941- mais moi le 14 décembre.Nous avions partagés la même classe de seconde aussi 1958-1959.A Dire Dawa,nous avions passées de belles vacances.Je suis très nostagique de ces temps.Mes plus sincères condoléances à toute le famille-bien que tardives.Que Dieu te bénisse mon ami!
February 27, 2022
February 27, 2022
Nous ne pouvons qu'imaginer les moments difficiles que vous continuez à traverser. Nous ne nous connaissions pas mais mes parents, Moolie et Berhane, étudiants à Paris à la fin des années 60, ont connu Gash Tadesse. Il faisait partie de ces personnes qui ont le don de distribuer du bonheur autour d'eux et de rendre chaque instant de la vie précieux. Au nom de notre famille, nous vous présentons nos sincères condoléances. A toi Lydia, notre grande sœur, tu peux compter sur notre soutien. Que sa belle âme repose éternellement en paix. Amen!
June 20, 2021
June 20, 2021
Chèr Tonton,
Je te remercie pour les meilleurs souvenirs qu'on passé ensemble en 2007 et 2018. Tu me donner des bons conseils et morales. La dernière fois, on parle sur le Viber, tu me dis que covid-19 attaque beaucoup Éthiopiens. Je ne sais pas que sera la dernière conversation téléphonique avec toi. I miss you so much.
I love you.
RIP
June 1, 2021
June 1, 2021
Ababio, it’s taken me a while to know what to write here. Your legacy is just that huge. I still don’t know how to pay tribute to the amazing light you were in all our lives. I know you know how dearly you are missed. Your jokes, your advice, your grace, the simplicity and purity of any interaction with you. Our conversations were usually loud hellos filled with laughter, very brief and yet meaningful. I miss you Ababio. May you rest in peace in the bright light you command with so much ease.
Love,
Kidio
April 5, 2021
April 5, 2021
Tadesse etait un ami d'enfance.Nous avons frequente le meme lycee et nous avons passe le baccalaureat ensemble.Et nous sommes partis ensemble dans le meme avion poursuivre nos etudes en France.
Quand nous etions adolescents Tadesse
qui avait une predilection pour la musique
et la danse se proposait souvent pour organiser des apres midi dansant.Nous faisions des contributions.Tadesse gerait
tout. Acheter des boissons douces se procurer un tourne disque a manivelle et des disques trouver une salle avec piste de danse et lancer des invitations surtout aupres des filles. Il faisait tout cela a la perfection.
Plus tard de retour au pays la revolution eclate et Tadesse etait devenu un ardent militant qui se depensait sans compter.Il avait des certitudes sur les changements
positives que le pays allait connaitre.Mais malheureusement la revolution qui a bouleverse le paysage politique du pays s'etait accompagnee d'experiences traumatisantes qui n'ont pas epargner des amis qui nous etaient precieux et chers.
L'itineraire sinueuse et complexe de la vie
n'ont pas ebranle Tadesse dans ses convictions de l'amitie et de ses valeurs
humanistes. Tadesse etait toujours la pour
les amis et meme au dela et face aux vicissitudes de l'existence il a su assumer ses responsabilites de pere de famille avec elegance et rectitude. Sa chaleur humaine nous manquera.

,
April 1, 2021
April 1, 2021
ከታዴ ጋራ የተዋወቅነው ከ50 ዓመታት በፊት በነሐሴ 1959 በአንደኛው የአውሮፓ ተማሪዎች ጉባዔ ላይ ነበር። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ በየዓመቱ ብንገናኝም፤ ቅርበት አልነበረንም። በቅርብ የተዋወቅነው በ1968 እና በ1969 ዓ.ም. በየካቲት 66 ት/ቤት እሱ አስተዳዳሪ ሆኖና እኔም አስተማሪ ሆኜ አብረን በሠራንበት ዘመን ነው። ግሩም አስተዳዳሪ እንደነበር አስታውሳለሁ። በተማሪዎችም ይሁን፣ በአስተዳደር ሠራተኞች ወይንም መምህራን አንድም ቀን አንድም ቅሬታ ቀርቦ አያውቅም።

ከአስተማሪዎቹ መካከል አብዛኞቻችን የመኢሶን አባሎች ነበርን። የድርጅት አባልነት ክፍያችንን ከደሞዛችን 10 ከመቶ ከምንጩ እየቆረጠ የት/ቤቱ ዳይሬክተር በነበረው በዶ/ር ተረፈ ወልደፃድቅ በኩል ለድርጅቱ የሚይስገባው ታዴ ነበር። ከጊዜ ወደጊዜ በፈቅድኝነት እንድናዋጣ የሚጠየቀውንም መዋጮ የሚሰበሰበው እሱ ነበር።

መኢሶን በነሐሴ 1969 የትግል ስልት ለውጥ ሲያደርግ ለጥቂት ወራት ተለያየን። በመጋቢት 1970 ወደአዲስ አበባ ስመለስ ሕይወቴን ያዳነ ጓደኛዬ እንደሚሆን አልሰብኩም ነበር። በዝያን ወቅት ከደርግ ፅጥታ ለመሰወር በየጊዜው መኖሪያዬን እለዋወጥ ነበር። ታዲያ አንድ ምሽት ሊቀበለኝ የተስማማ አንድ ጓድ ቤቱን ዘግቶ ይጠፋል። አማራጭ ሥፍራ ስላልተዘጋጀ አሁንም እዝያው አዲስ አበባ በሕይወት ካለው ጓድኛዬ ጋራ የምናደርገው ይጠፋብናል። በተለይም የሰዓት ዕላፊው ከመድረሱ በፊት መዘየድ ነበረብን። ታዴ ዘንድ አድርሰውኝ ወደየዋሻቸው እንዲገቡ ተስማማን። ሹፌሩ የ መ/ቤት ባልደረባ የነበረው ኢብራሂም ነበር።

የታዴን በር አንኳኳሁ። ከፊቱ ተግትሬ ሲያየኝ ምንም አልተደናገጠ። "Welcome" ብሎ ከመኝታ ቤቱ አስገባኝ። "እዚህ ማደር ብትችል መዋል አትችልም" አለ። ጥቂት ከተወያየን በኋላ ሁለታችንም በቅርብ ለምናውቀው የየመን አምባሳደር መደወሉ እንደሚሻል ተስማማን። ደወለላቸው። አምባሳደሩ "አሁኑኑ ይምጣ" አሉ። አደረሰኝ።

ከዚህ በኋላ ከታዴ ጋራ የተገናኘነው ከበዙ ዓመታት በኋላ ፓሪስ ለወገቡ ህክምና መጥቶ ሳለ ነበር። ከእህቱ ከምንትዋብ ቤት ወላል ላይ ተጋድሞ አገኝሁት። ልክ ትላንትና የተለያየን ያህል ጭውውታችንን ቀጠልን። በፓሪስ ስንገናኝም ሆነ ከ2008 ዓ.ም. ጀምሮ በአዲስ አበባ በዓመት ሦስት አራት ጊዜ ስንገናኝ ስለዛች የ1970 ምሽት አንስተን አናውቅም። ውይይታችን ይልቁኑ ስለየወቅቱ የአገሪቱ ሁኔታ ነበር። ዛሬ ተመልሼ ሳስበው የድርጅታዊ ግዴታ አድርገን ስለወሰድነው ይመስለኛል።

ታዴ ግሩም ጓድ ነበር። ደግሞም በጣም ደግና ግሩም ማኅበራዊ ተካፋይ።

በሰላም ይረፍ።
አንዳርጋቸው አሰግድ

April 1, 2021
April 1, 2021
A big and unexpected loss. Since I came to closely know him thirty years ago, Tadesse was inspiring in terms of maintaining social relationship. Let him REST IN PEACE
March 31, 2021
March 31, 2021
Tade was a gem and one of a kind! A favorite cousin that I loved dearly and will miss beyond measure. He was the most loving, caring, and compassionate person who never failed to check on my family’s wellbeing. It breaks my heart to realize that I will not receive his “Endegena Tefash Demo” texts or phone calls. I will treasure his memories and he will forever be in my heart.

Wishing peace and comfort to Amaru, Minte and children. May Tade's memory always be a blessing!!
March 30, 2021
March 30, 2021
Salut Tonton,

Que d’histoires vécues ensemble, que d’anecdotes, que de moment partagés que je n’oublierais jamais.....Merci pour tout.

Merci d’avoir été une source d’inspiration, un guide, d’avoir incarner avec brio la figure tutélaire que je recherchais tant.....Merci.

Merci pour ton humour unique, tes blagues et histoires qui, même après la énième écoute, faisaient toujours leurs effets. Merci d’avoir été un modèle de «Cool uncle »......Merci.

Merci de m’avoir encourager à voir plus loin, à remettre en question mes conceptions, à m’instruire quand je ne connaissais pas, toujours avec la plus grande des bienveillances.......Merci, merci pour tout Tonton.
March 28, 2021
March 28, 2021
I met Tadesse in 1973 /74 in Paris as a young student at Mentewab’s place . He was on his way to Addis at that time . I will always remember how he animated the evening with his beautiful voice by singing well known Ethiopian lyrics . When I returned to Ethiopia after 42 years I found Tadesse in rotary club Entoto . It is during this time that I managed to know Tadesse better . I found him very generous , knowledgeable and at the same time funny and very approachable . We worked together in supporting Addis Fire School and I noticed his personal commitment for humanitarian work and his strong engagement in teaching the young generation to become good citizens for their country . Tadesse left us unexpectedly and we were all shocked by his sudden death . May his soul Rest In Peace
Teguest
March 28, 2021
March 28, 2021
My sincere condolences to Tadesse’s wife Amaru, his sister Mentewab and his children and grandchildren. Tade was unique in more than one way. Always ready to share his knowledge and ready to help in his own generous way. Tade was one of the most caring and reliable persons in my circle of friends. I miss his wisdom. I miss his endless desire to learn and share. I miss his regular calls to check on my well-being and his offer to support me with the scholarship for blind university students. I miss Tade, my friend for 50 years and the one who introduced me to Rotary! As we say in French “bon vent”!
March 27, 2021
March 27, 2021
ታደሰ ሁለ ገብ ስዉ. መጀመሪያ ያገኘሁት, በ 1952, የልስዬ ፓርቲ አለ ተብለን ስንሄድ አንድ ልጅ
   እኔ አንድያ ስወድሽ ስንገበልሽ
    ለማይረባሽ ትዳር ጥለሽኝ ኮበለልሽ
አያለ የዳሊዳን ሲዘፍን አደነቅን... ያልጅ ታዴ ነበር
ከዛ በኃላ በፈረንሣይና በኢትዮጵያ, በሥራ ሆነ በፖለቲካ አብረን ሰርተናል አስከ አረፍቱ ሳምንት ድረስ ብያንስ በሳምንት አንዴ ይደውልልን ነበር. ሃና ጋ ሲደውል 'ሽማግልየዉ አለ?' አያለ 'ያሞግሸኝ' ነበር. ያጎድለናል!!!
ልባለብይቱና ልጆቹ መጥናናትን አመኛለሁ!!!!
March 27, 2021
March 27, 2021

ታደሰ የሃምሳ አመት ወዳጄ ፣ እንደ ታላቅ ወንድሜ ፣ መካሪዬ ነበር። ይህ ክፉ በሽታ ታደሰንም፣ እንደ ብዙ ወንድሞቻችን ባልጠበቅነው መንገድ እና ግዜ ነጠቀን።
ታደሰን በአንድ ቃል ግለጽ ብባል የሚመጣልኝ ቃል “ስብዕና”፣ “ትልቅ ስብዕና” ነው።  ታደሰ ገና በወጣትነት እድሜው የሊሴ ገብረ ማርያም ጓደኞቹን በማስባሰብ አብረው እንዲደሰቱ ፓርቲዎች ማዘጋጀት፣ ሙዚቃ ማዳመጥ ይወድ ነበር እየተባለ ይነገርለታል። በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ ሲዘፍን፣ ሲገጥምም በአርምሞ ይደመጥ ነበር ። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ሌሎችን ማስባስብ ማስተባበር እና በልዩ ልዩ መድረኮች የማሳተፍ ፍላጎት እና ልዩ ስጦታ የመለያ ጠባዩ ነበር።
በስልሳዎቹ በፈረንሳይ አገር ተማሪ፣ በኋለም ሰራተኛ በነበረበት ዘመን፣ በአገሩ የሚኖሩትን ኢትዮጵያውያን ተማሪዎችን በማገናኘት “በፈረንሳይ የኢትዮጵያ ተማሪዎች ማህበርን” ለማቋቋም እና ለማደራጀት፣ ከፍ ያለ ሚና ተጫውቷል። እንዲሁም በአውሮፓ የኢትዮጵያ ተማሪዎች ማህበር ዘርፈ ብዙ እና ክፍተኛ አስተዋጽኦ ለብዙ አመታት አበርክቷል።
ፈረንሳይ የኢትዮጵያ ተማሪዎችን ማህበር በመወከል ፣ ፌያንፍ (FEANF) በሚባል በፈረንሳይ የአፍሪካ ተማሪዎች ማህበር ሰፊ ተሳታፊነት ነበረው። በዘመኑ በፓሪስ አብረውት ከነበሩት የትግል ጓዶቹ እነ ሃይሌ ፊዳን፣ ዳንኤል ታደሰን መጥቀስ ይቻላል። አልፋ ኮንዴን የጊኔ ኮናክሪ ፕሬዚደንት ፣ ከቡሩንዲ ኒኮላ ብዋኪራ (ነፍስ ይማር፣ ካረፈ ወር ሆነው) ፣ ከቶጎ ጆአኪም አቦብሊ (የዛሬ 13 አመት ሲያርፍ ታደሰ በቀብሩ ስነ ስርአት ሎሜ ተገኝቶ ነበር) ፣ የፌአንፍ ጓዶቹ እና በኋላም የቁርጥ ቀን ጓደኞቹ ነበሩ።
ዘመኑ (እንደ አውሮፓ አቆጣጠር በ1960 አካባቢ) አልጄርያውያን ለነጻነታቸው ከፈረንሳይ መንግስት ጋረ በትግል ላይ የነበሩበት ነበር። ታደሠ ለትግላቸው ያለውን እምነት እና አጋርነት በመግለጽ አብሯቸው ይታገል ነበር ። ክቪየትናም እና ላኦስ ታጋዮችም ጋር በተመሳሳይ በመተባበር ለአለም ጭቁን ህዝቦች ያለውን ወገናዊነት እና የትግል አንድነት በሚገባ ተወጥቷል።
የታደሰ ለሰው ልጅ ያለውን ፍቅር ፣ ለተጨቆኑ፣ ለተበደሉ፣ ፍርድ ለተነፈጉ፣ ለተራቡ፣ ለታረዙ ያለውን ወገናዊነት በብዙ መንገድ፣ በአስተሳሰቡ ፣ በበጎ አድራጎቶቹ አሳይቷል ፣ ዋና ዋናዎቹን ለማስታወስ ፣
• ፈረንሳይ በነበረበት ጊዜ በ1973ቱ ረሃብ የተጎዱትን ወገኖች ለመርዳት ዕርዳታ የማሰባሰብ ስራ፣
• በደርግ እስር ቤት የሚማቅቁ ጓዶች እና ሌሎችም የደርግ ሰለባዎችን እየተመላለሰ በመጠየቅ፣ ምግብ እና መጻህፍት በማቅረብ ፣ ብዙ ሰው በፍርሃት ወይም በአድር ባይነት፣ ወይም በሁለቱም ምከንያት፣ አልስማሁም፣ አላየሁህም እያለ መንገድ ለውጦ በሚሄድበት ዘመን ፣ ታደስ ለጓዶቹ ብቻ ሳይሆን ለሁሉም ተጎጂዎች አይዞችሁ ማለትንና በሚችለው ሁሉ መርዳትን የተለየ ተልዕኮው አድርጎት ነበር ። በተለይ አ/አ ስንቅ የሚያቀርብ ዘመድ ለሌላቸው እስረኞች የተለየ እንክብካቤ ያደርግ ነበር። የታሳሪዎችን ቤተሰቦች ይጠይቅ እና ይንከባከብ ነበር፣ በዚህም የብዙሃን አክብሮት እና ፍቅር ነበረው።
• ለሌሎች ሰዎች ባለው ፍቅር እና እንክብካቤ ደንታ (Care) በብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ ጽሁፎችን እና ድህረ ገጾችን በመመርመር ፣ በማዛመድ እና በማጠናከር ፣ ከሃገራችን ሁኔታ እና ባህል ጋር በመዋሃድ ፣ ከራሱም የህይወት ልምድ ጋር በማዛመድ ሰለ መልካም አመጋገብ ፣ በጤና እና በአመጋገብ መሃል ስላለው መተሳሰር ፣ በተለይ የሱካር ታማሚዎች ፣ የኩላሊት ታማሚዎች ማድረግ ስለሚገባቸው ጥንቃቄ ሁለት ጠቃሚ እና ሁሉም ሰው አንብቦ ሊረዳቸው ፣ ሊረዳባቸው የሚችሉ መጽህፍት ለአንባብያን አበርክቷል።
• ታደሠ ከጻፋቸው መጽሃፎች አንዱ “ብሩህ ዜጋ ማነጽ” የሚባል ነው። ታደሰን እንደ ብዙ ሰዎች ሁሉ የሃገራችን ሁኔታ በእጅጉ ያሳስበው ነበር። በተለይ የወጣቶች ስራ አጥነት፣ የባህል መዛባት፣ የስነ ምግባር መደብዘዝና አላማ ቢስነት የጭንቀት ነጥቦቹ ነበሩ ። ሰለዚህም ከሌሎች በመለየት፣ በ96 ገጾች እና በ 24 የምክር አርዕስቶት የተካተተ መጽሃፍ የዛሬ ሁለት አመት በነጻ ለወጣት አንባቢያን አበርክቷል። የመጽሃፉን ብሩህ ሃሳቦች እና አላማ፣ ታደሰን ወጣቱን ትውልድ ለማነጽ ፣ለማበራታት እና ለማጎልመስ፣ የነበረውን ጽኑ ፍላጎት ይገልጻል ።
• የታደሰ ሌላው ጠባይ ማህበራዊነት ነው። ሰዎችን ማገናኘት ፣ የተለያያ ሃሳብ ያላቸው ሰዎች እንዲወያዩ፡ ተባብረው እንዲሰሩ ፣አብረው እንዲዝናኑ፣ በማህበር ፣በመተባበር እንዲረዳዱ የማድረግ የተለየ ተሰጥዖ እና ፍላጎት ነበረው። ለዚህም የተከበረ ጊዜውን አበርክቶ ዘክሯል። እንደ ምሳሌ ለመጥቀስ ፣ የቀበሌ 19ን የቼዝ (Chess Club) እና የቡል (Pétanque) ክለብ፣ የኢትዮጵያ ቼዝ (ሰንጠረጅ )ፌዴሬሽን ፣ የቀበሌ 19ን የሸማቾች ማህበርን በማቋቋም ረድቷል። በሮታሪ (Rotary Club Addis Abeba Entoto) በአባልነት፣ በሊቀመንበርነት ያደረገው እስተዋጽዖ ለዘላለም ህያው ያደርገዋል።
• እንዲሁም ቀደም ሲል በአፍሪቃ የሸማቾች ማህበር ፌዴሬሺን ዲሪክተርነት (ዚምባብዌ)፣ በትራንስፓራንሲ ኢንተርናሽናል አባልነት፣ የኢትዮጽያ ሸማቾችን ማህበር ለማቋቋም ያደረገው ከፍተኛ ጥረት ይሄንኑ ስብዕናውን፣ ደግነቱን ( Generosity) ለብዙሃን ፍላጎት እና ጥቅም ያለውን መቆርቆር እና ወገናዊነት የሚመሰክር ተጨማሪ እውነት ነው።
• የዛሬ አመት ታትሞ የተሰራጨው የታደሰ የመጨረሻ መጽሃፍ “የገጠሙኝ አስቂኝና አሳሳቢ ሁነቶች” ይሰኛል። ይህ በስብዕና እና በፌዝ (Humor) ያጌጠ መጽሃፉ ፡ በጎ እና ክፉ የህይወት ገጠምተኞቹን ፡ በህይወት ያሉ እና የሌሉ ወዳጆቹን እና ሌሎችንም የሚያስታውስበት፣ የሚወድስበት፣ እንደ ህይወት “ኑዛዜ” ሊቆጠር የሚችል ጽሁፍ ነው።
ለባለቤቱ ለአማረች ፣ ለልጆቹ ሊዲያ፣ መብአ ፣ የሺአረግ፣ እምዩ እና ህሩይ፣ ለእህቱ ለምንትዋብ እንዲሁም ለወዳጅ እና ዘመዶቹ መጽናናትን እመኛለሁ።
ታዴ በልባችን ለዘላለም ይኖራል።
ዘሪሁን ተክሌ፣ 27/03/2013
March 26, 2021
March 26, 2021
Remembering Tade ( Ababi ) He is gone a better place forever. But his wisdom, full of knowledge in any topics ( my favorite ones are Ethiopan history and wellness ) his kindness, loving and caring personality for the people around him will be missed dearly.
I am at a loss of words to say thank you for welcoming us ( my children and I )at any time with a great hospitality and unforgettable memories.
May Your Soul Rest In Peace.
March 26, 2021
March 26, 2021
Those we love never leave us,
they will always walk amongst us.,
every day unseen unheard
But always near
Still loved
Still missed
And very dear.
Love and miss you much Tadye.

Leave a Tribute

Light a Candle
Lay a Flower
Leave a Note
 
Recent Tributes
January 15, 2023
January 15, 2023
በዛሬው ቀን የታዴን ሁለተኛ የሙት አመት በማክበር ወንድማችንን እንድናስታው ተሰብሰበናል ፣ አወን ሁለት አመት ሆነ ታዴ ከተለየን ፣ የዛሬ ስድስት ወር ገደማ ፣ አዲስ ፍሬ  ት/ትቤ በታዴ ስም የጽሃፍት ቤቱን ሲያመርቅ ያነበብኩትን አጭር ጽሁፍ ከዘመድ ወዳጆቹ ጋር በመቋደስ የታዴን በጎ ስራዎች ማስታወስ ደስታዬ ነው ፣
ዘሪሁን ተክሌ .፣ ጥር 7 ፣ 2015

በአዲስ ፍሬ አንደኛ ደረጃ ት/ቤት ታደሰ ገሰሰ መጽህፍት ቤት ምረቃ/ 8 ጁን 2022.

ወንድማችን ታደሰ ከተለየን ሰነበተ ፣ አመት ፣ አመት ተኩል አለፈው....አሁንም ለዘላለም እንደተለየን ልቀበለው አልቻልኩም ፣ አልፈለኩም ፣ አሁንም ቀበሌ 19 ፣ የቼዝ ገበታው ፊት፣ በአርምሞ ሲያስብ ይታየኛል ፣፣

ከታደሰ ምንም ጊዜ የማልረሳው እንድ ትልቅ ቁም ነገር አለ ፣ ከሚወዳቸው ጥቅሶች አንዱ “ ደግነት ለራስ ነው ” የሚለው ነው ፣ ከዚህ ጥቅስ ጋር አንድ የተለየ ታሪክ አለኝ ፣ ታደሰ በብዛት እና በአይነት የላቁ የፊልም ፣ የሙዚቃ፣ የመጽሃፍት ፣ የልዩ ልዩ መጣጥፎች እራሱ የጻፋቸው እና ከሌሎችም ደራስያን የሰበሰባቸው ሰፊ ኮሌክሽን እንዳለው ብዙ ሰው ያውቃል፣፣ በየጊዜው የተወሰኑ የፊልም አይነቶች፣ አንዳንድ ዘፈኖች ፣ ከጻፋቸው ጽሁፎች የወቅቱን ሁኒታ ያብራራሉ ብሎ የሚገምታችውን በሲዲ ፣ በሜሞሪ ስቲክ እየቀረጸ ይሰጠኛል ፣ እንድ ቀን እንደውም በሙሉ የሃርድ ዲስኬን እንዳለ ለምን አልገለብጥልህም፣ ከፍ ያለ የክምችት ካፓሲሲቲ ያለው ኤክስተርናል ዲስክ ይዘህ መጥተህ በሙሉ ያሉኝን ፋይሎች ልገልብጥልህ አለኝ ፣ እኔም በደስታ ተቀበልኩት ፣ ይሰነብትና የታደሰ ኮምፑተር ይሰረቃል ፣ ታደሰም ይደውልና “ደግነት ለራስ ነው ብዬህ የለ ፣ ኮምፑተሬ ተሰርቆ ሌላ ኮምፑተር ገዝቼአለሁ ፣ በል ፋይሎቼን መልስ “ አለኝ ፣፣ ከዚህ ያገኘሁት ትምህርት ፣ ደግነት ለአድራጊው ከሚሰጠው ደስታ እና ጸጋ ጋር አድራጎቱ ይዋል ይደር አንጂ ተመልሶ ለደግ አድራጊው ፣ ለባለቤቱ የሚመጣ መሆኑን ነው ፥፣ አሁንም አንድ ሰው ከመንገዱ ወጥቶ ለሌላው ሰው በጎ ነገር ሲሰራ ሳይ ፣ የታዴ ምስል ከፊቴ ድቅን ይላል ፣፣

ከሮታሪ ክለብ አዲስ አበባ እንጦጦ ወንድሞቹ እና እህቶቹ ጋር የአዲስ ፍሬ ት/ትቤን ለተማሪዎቹ ፣ ለመህራን፣ እንዲሁም ባጠቃላይ ለት/ቤቱ ማህረሰብ ምቹ ለማድረግ ታዴ ያላደረገው ጥረት የለም ፣ ለዚህም የአዲስ ፍሬ ማህበረሰብ ለታዴ ያለው አክብሮት እና ፍቅር ህያው ምስክር ነው፣፣ በተለይ ለትምህርት ጥራት ፣ ለእውቀት መዳበር የነበረው ጥጽኑ እምነት እና ጥረት የላቀ ነበር ፣ የት/ቤቱ መጻህፍት ቤት በወንድማችን በታደሰ ስም መሰየሙ ትክክል እና ተገቢ ነው ፣ ይህን በማድረግ መልካም ፈቃደኝነታቸውን እና ድጋፋቸውን ለሰጡን ለት/ቤቱ አመራር እና መምህራን ምስጋናችን ከፍ ያለ ነው፣ ይህ መጽሃፍት ቤት በት/ቤቱ ውስጥ ተገቢ ቦታውን ይዞ ‘’የእውቀት ማእከል’’ እንዲሆን የተቻለውን ጥረት ለማድረግ በሮታሪ ክለብ አዲስ አበባ እንጦጦ ስም ቃል እገባለሁ ፣፣

የታደሰን ነብስ በገነት ያኑርልን ፣፣

ዘሪሁን ተክሌ ፣ ሮታሪ ክለብ አዲስ አበባ እንጦጦ፣ የ2021/2022 ሊቀ መንበር
April 8, 2022
April 8, 2022
Nous étions dans la même classe de 1ère 1959-1960 et j'ai appris de ton décès en m'inscrivant à l'association des anciens élèves du Lycée Guebre Mariam d'Addis.
En 1958, mon père dirigeait la fabrique de coton à Dire-Dawa appartenant au Prince de Harar.
Nous nous sommes rencontrés à Dire-Dawa avec d'autres camarades de l'école dont Gaetano Trimarchi et Merzian.Nous sommes nés la même année 1941- mais moi le 14 décembre.Nous avions partagés la même classe de seconde aussi 1958-1959.A Dire Dawa,nous avions passées de belles vacances.Je suis très nostagique de ces temps.Mes plus sincères condoléances à toute le famille-bien que tardives.Que Dieu te bénisse mon ami!
February 27, 2022
February 27, 2022
Nous ne pouvons qu'imaginer les moments difficiles que vous continuez à traverser. Nous ne nous connaissions pas mais mes parents, Moolie et Berhane, étudiants à Paris à la fin des années 60, ont connu Gash Tadesse. Il faisait partie de ces personnes qui ont le don de distribuer du bonheur autour d'eux et de rendre chaque instant de la vie précieux. Au nom de notre famille, nous vous présentons nos sincères condoléances. A toi Lydia, notre grande sœur, tu peux compter sur notre soutien. Que sa belle âme repose éternellement en paix. Amen!
His Life

Text read at the ceremony by Mr.Yeraswork Admassie ( Amharic version )

March 3, 2021
የአቶ ታደሠ ገሠሠ ትውስታ
ወንድማችን ታደሠ ገሠሠ ሰኔ 14 ቀን 1933 ዓ/ም ከእናቱ ከወ/ሮ የሺሐረግ ይርዳውና ከአባቱ ከአቶ ገሠሠ
ተድላ በአዲስ አበባ ከተማ ጎላ ሰፈር ተወለደ፡፡ የተወለደው ሀገራችን ነፃነቷን መልስ በተቀዳጀት ማግሥት ከወር
ተኩል በኋላ ብቻ በመሆኑ ሳይሆን አይቀርም ወላጆቹ “ታደሠ” ብለው የሰየሙት።
ታደሠ፣ ሰባት ዓመት እስከሚሆነው ድረስ ሐረር ከተማ በአያቱ ሰፊ ቤት ከእህቱና ከአጎትና አክስት ልጆቹ ጋር
በደስታ አደገ።
ከዚያም ወደ አዲስ አበባ ተመልሶ የ1ኛና 2ኛ ደረጃ ትምህርቱን በሊሴ ገብረማርያም ት/ቤት ተከታተለ፡፡
ወጣቱ ታደሠ በአገር ቤት ትምህርቱ መጨረሻ ላይ፣ በ1952 ዓ/ም በኮንጎ ነፃ መውጣት ሳቢያ የተፈጠረውን
ብጥብጥ ለማርገብ ወደዚያ የተላከውን የኢትዮጵያ ጦር በአስተርጓሚ ኦፊሴርነት ተቀላቅሎ በመዝመት፣
እስከ ሕይወቱ መጨረሻ የዘለቀውን አና መለያ ጠባዩ የሆነውን ማኅበረሰባዊ አክቲቪዝም “ሀ” ብሎ ጀመረ።
ከሊሴ ገብረማርያም ከተመረቀ በኋላ የነፃ ትምህርት እድል አግኝቶ በፓሪስ ከተማ በሚገኘው ዕውቁ
ዩኒቨርስቲ በመግባት የዩኒቨርስቲ ትምህርቱን ተከታትሎ የመጀመሪያ ዲግሪውን ተቀበለ። በመቀጠልም
በሌላው ዕውቅ ኤኮል ሱፔሪየር ጂ ኢኮኖሚ ሁለተኛ ዲግሪነውን በኢኮኖሚክስ ሰራ፡፡ በመቀጠልም ለሁለት
አመታት በዚያው በፖራል በማኔጅመንትና በኢንፎርሜሽን የሥራ ዘርፍ ተሰማርቶ ልምድ አካበተ።
በአውሮፓ/ ትምህርቱን በመከታተል ላይ በነበረበት ጊዜ ከትምህርቱ በተጓዳኝ፣ ሃገሩንና አህጉሩን በተመለከተ
በወቅቱ በነበሩ እንቅስቃሴመ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል። በተለይ፤
1ኛ/ በአውሮፓ የኢት ተማሪዎች ማኅበር የመፅሄት ቦርድ አባል
2ኛ/ በፈረንሳይ የኢት ተማሪዎች ማኅበር ሥራ አ/ኮሚቴ አባል
3ኛ/ በፖሪስ የኢትዮጵያ ተማሪዎች ማኅበር ሥ/አ/ኮማቴ አባል ሆኖ አገልግሏል፡፡
በተጨማሪ፡- በፈረንሳይ የአፍሪካ ተማሪዎች ማኅበር አመራር ውስጥ አባል ሆኖ ወደ ሁዋላ በየአገሮቻቸው
ፖለቲካ ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ ካሳደሩ ወጣት አፍሪካውያን ጋር ጎን ለጎን ሆኖ ሠርቷል።
ታደሠ፣ ከአውሮፓ ቆይታው በጉዋላ ወደ ውድ ሃገሩ ተመልሶ በተለያዩ መንግሥታዊ፣ ዓለም አቀፋዊ እና
መንግሥታዊ ባልሆኑ ድርጅቶች ውስጥ መደበኛ ሠራተኛ በመሆን ለሁለት ዓሠርተ-ዓመታት አገልግሏል።
ከነዚህም መሥሪያ ቤቶች ዋናዎቹ፡-
- የየካቲት 66 የት/ቤት
- የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
- በኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የቴክስታይል ኮርፖሬሽን
- በአ/አ የተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ ኮሚሽን መሥሪያ ቤት ሲሆኑ በተጨማሪ በዝምባቡዌ
አህጉራዊ የሸማቾች መስሪያ ቤት አገልግሏል።
ከኢ-መደበኛ ሥራ ውጭም በትርፍ ጊዜው በበርካታ የማኅበረሰብ ድርጅቶች ውስጥ አስተዋጽኦ አድርጉዋል።
ከነዚህም ዋና ተጠቃሾቹ የሚከተሉት ናቸው-።
- የኢትዮጵያ ቼስ ፎደሬሽን መስራች እና ለረዥም ጊዜ የአመራሩ አባል፤
- የቡል ጨዋታ በኢትዮጵያ እንዲለመድ ሲል የቡል ክለቦች መስራች እና አነቃቂ፤
- የኩላሊት ማጠቢያ መሳሪያ በብዛት ወደ ሃገር በማስገባት ረገድ ከፍተኛ ሚና የተጫወተው የኩላሊት
ሕሙማን መርጃ ማህበር አመራር አባል፤
- የሮተሪ ክለብ ንቁ አባል፤ እና
- ከአዲስ አድማስ መስራቾች እና መሪዎች አንዱ ነበር።

በተጨማሪ፤ ታደሠ አራት መፃሕፍት እና በርካታ መጣጥፍ ደርሶ አሳትሟል። ከነዚህም ውስጥ ሁለቱ
በጤና እና በጤናማ አመጋገብ ላይ ያተኰሩ ጠቃሚ መፃሕፍት ናቸው።
ታደሰ የቤተሰብ ሰው፥ ቁምነገረኛ እና ለወዳጅ ዘመዱ ቀደሞ ደራሽ፥ የዕርዳታ ሥራ ቀስቃሽ እና አደራጅ
የነበረ ሲሆን፤ የዚያኑ ያህል ደግሞ የደስታ እና የጨዋታ ሰው በመሆን በራሱ ጭምር የመቀለድ ተሰጥዎ
ያለው ነበር።
ዛሬ ወንድማችን ታዴን የምንሰናበት ቀን ነው። ሆኖም በመለያዬታችን የምናዝንበት ብቻ ሳይሆን፥ ረዥም
ፍሬያማ ህይወቱን የምንዘክርበትና ለቤተሰቡ መፅናናትን እና መልካሙን የምንመኝበት አጋጣሚ ነው።
ስለሆነም፥ ለመላ ወዳጅ ዘመዱ፤ በተለይም ለባለቤቱ ወ/ሮ አማረች ክፍሌ፥ ለእህቱ ወ/ሮ ምንትዋብ፥
ለልጆቹ ሊድያ፣ መብአ፣ የሺሃረግ፣ ሕሩይ እና እሙዬ፤ እንዲሁም ለሦስቱ የልጅ ልጆቹ ፈጣሪ መፅናናትን
እንዲሰጣቸው እና እንዲጠብቃቸው እንመኛለን።
በመጨረሻ፤ ጊዜ የጣለብን ወረርሽኝ እስከሚወገድ ድረስ ቀናቶችን በጥንቃቄ ለማሳለፍ ስለምንገደድ፤
የስንብቱን ሥርዓቱን በዚሁ ቋጭተን መበተን የኖርብናል። ትናንትና ማታ ላይ ባለቃ ጊዜ ለዛሬ ተዘጋጅቶ
የነበረውን የጠበል ፀዲቅ ሥርዓት በዚህ ህሳቤ እንዲሰረዝ እንደተደረገው፤ ለሃዘነተኛው ቤተሰብ ደህንነት
በማሰብ ሃዘናችንን ለመግለፅም ሆነ ለማፅናናት ወደ ቤተሰቡ መኖሪያ በመሄድ ቆይታ ከማድረግ
እንድንቆጠብ አደራ እንላለን።
ቤተሰቡ፤ በዚህ በመገኘት የሃዘኑ ተካፋይ የሆናችሁትን ሁሉ ከልብ ያመሰግናል።

Text read at the ceremony by Mr.Yeraswork Admassie ( English version )

March 3, 2021

Our dear brother Tadesse Gessesse was born on the 21st of June 1941 from his mother Yeshihareg Yirdaw and his father Gessesse Tedla in Addis Abeba. He lived at his grandmother house in Harar until he was seven years old with his uncle, his sister and other siblings. He led a happy childhood.
Then, he returned to Addis Abeba and finished his primary and secondary school studies in Lycee Guebre Mariam. In 1952, he went to Congo with the Ethiopian peacekeeping troops and participated in peacekeeping missions in the country as a translator.

After returning to Ethiopia and graduating from Lycee Guebre Mariam, he went to France for higher education and received his Master’s degree in Development Economics. As a university student, he was profoundly concerned by Ethiopian and African current affairs, and he was an active member of many Ethiopian and African student associations. He was able to work closely and exchange ideas with other Africans who have achieved great things in their respective countries today. He then worked for 2 years in management and Information technology fields.

In 1967, he returned to Ethiopia and worked in various governmental organizations and private companies for the following 20 years or so, such as the ministry of foreign affairs, Yekatit 66 school, UNDP, UNECA, Consumers International etc...

In his free time, he participated in many community projects as that was one of his greatest ambitions in life. He founded the Ethiopian Chess Federation and was the Chairman for many years. He also built Petanque courts in an effort to encourage elder members of the community to stay active. He played a big role in an Ethiopian association who imported several dialysis machines in order to help those who suffer from kidney failure. He was an active member in the French Rotary and has participated in multiple caritative missions in Ethiopia.He was very generous and always looked for ways to help people and better the community.

In addition, Tadesse has published 4 books in total, of which two were health related, as well as many interesting articles around various subjects. He was passionate about the origin of mankind, space, health, charity, bettering the community and always preached about tolerance and love. He was very reliable and always there for the people he loved. He lived a full life and always made jokes, sometimes even about himself. He had a very positive mindset. He had five children, and three grandchildren.
Recent stories

Mon frère

March 20, 2021
                                Mon frère,
                      Toi avec qui je partage
                         Conversations et
                  Messages, tu sais, dans un
                      Sourire me rassurer,
                       Je suis toujours là
                          Pour t'écouter.
                             Proche ou
                     Loin de mon histoire.
                         Je serai toujours là
                    pour toi comme tu le
                  Seras toujours pour moi.
March 20, 2021
ታዴ
አንተን ማጣት ከባድ ነው፡፡ እኔ በዝምታ አንተ ግን የቤቱ ድምቀት ነበርክ፡፡ ያለ አንተ ቤቱ ባዶ ነው፡፡
አሁን ግን ዝምታዎች የውስጤን ሐዘን እና ለቅሶ ሊገልጹልኝ አልቻሉምና በጽናት የቆምንባቸው ከፍታና ዝቅታን ያየንባቸው በሁሉም ሁኔታ አብሮ ለመኖር የገባነው ቃል ኪዳን ላጸናንባቸው 30 ዓመታት ለእኔ የሕይወትትምህርት ቤት ናቸው፡፡ በሁሉም ሁኔታ አብረኸኝ በመዝለቅህ ምስጋናዬ ለአንተ ነው፡፡ በነፃነት እንድኖር ፈቅደህ ሁሌም እንደፈለግሽ ብለህ በመውጣት በመግባቴ ሁሉ ሰላም እንዲሰማኝ ስላደረግኸኝ አመሰግናለሁ፡፡ 
በአንተና ከአንተ ባፈራናቸው ልጆች በተለወጠው ሕይወቴ ያለ ስስት የሰጠኸኝ ፍቅር የሕይወቴ ስንቆቼ ናቸው፡፡ በጠዋት ስትወጣ ድምፅህ ማታ ስትገባ ሙሉ የሆኑቱ እጆችህ ሁሌም በትዝታ ከኔው ጋ ናቸው፡፡ የምትሰጠው ፍቅር በልብህ ሙሉ ሆኖ እንደሁሌው ያለህን ለመስጠት እጅ ሳይያጥርህ አንተ የሁሉ ወዳጅ በድንገት ሳናስበው ብትለየንም ሁሌም በልባችን ከኛው ጋ ነህ!
እስከ መጨረሻው ያንተው ውድ ባለቤትህ
March 26, 2021
Tadouye,

Je voudrais d'abord te remercier pour l'enfance hors du commun que nous avons tous eu. Non seulement tu as toujours été là pour nous, mais pour tout ceux qui en avaient besoin. Les valeurs par lesquelles tu vivais tous les jours et ta générosité interminable se reflètent dans chacun de tes enfants et les effets de ton absence se remarquent de plus en plus avec le temps.
À entendre tes histoires de tes proches, c'est clair que tu as eu ce même effet sur tous ceux qui te connaissaient.
J'espère que tu seras toujours fier de nous comme nous le sommes d'avoir eu un père comme toi.

Invite others to Tadesse's website:

Invite by email

Post to your timeline