ForeverMissed
Large image
His Life

Text read at the ceremony by Mr.Yeraswork Admassie ( Amharic version )

March 3, 2021
የአቶ ታደሠ ገሠሠ ትውስታ
ወንድማችን ታደሠ ገሠሠ ሰኔ 14 ቀን 1933 ዓ/ም ከእናቱ ከወ/ሮ የሺሐረግ ይርዳውና ከአባቱ ከአቶ ገሠሠ
ተድላ በአዲስ አበባ ከተማ ጎላ ሰፈር ተወለደ፡፡ የተወለደው ሀገራችን ነፃነቷን መልስ በተቀዳጀት ማግሥት ከወር
ተኩል በኋላ ብቻ በመሆኑ ሳይሆን አይቀርም ወላጆቹ “ታደሠ” ብለው የሰየሙት።
ታደሠ፣ ሰባት ዓመት እስከሚሆነው ድረስ ሐረር ከተማ በአያቱ ሰፊ ቤት ከእህቱና ከአጎትና አክስት ልጆቹ ጋር
በደስታ አደገ።
ከዚያም ወደ አዲስ አበባ ተመልሶ የ1ኛና 2ኛ ደረጃ ትምህርቱን በሊሴ ገብረማርያም ት/ቤት ተከታተለ፡፡
ወጣቱ ታደሠ በአገር ቤት ትምህርቱ መጨረሻ ላይ፣ በ1952 ዓ/ም በኮንጎ ነፃ መውጣት ሳቢያ የተፈጠረውን
ብጥብጥ ለማርገብ ወደዚያ የተላከውን የኢትዮጵያ ጦር በአስተርጓሚ ኦፊሴርነት ተቀላቅሎ በመዝመት፣
እስከ ሕይወቱ መጨረሻ የዘለቀውን አና መለያ ጠባዩ የሆነውን ማኅበረሰባዊ አክቲቪዝም “ሀ” ብሎ ጀመረ።
ከሊሴ ገብረማርያም ከተመረቀ በኋላ የነፃ ትምህርት እድል አግኝቶ በፓሪስ ከተማ በሚገኘው ዕውቁ
ዩኒቨርስቲ በመግባት የዩኒቨርስቲ ትምህርቱን ተከታትሎ የመጀመሪያ ዲግሪውን ተቀበለ። በመቀጠልም
በሌላው ዕውቅ ኤኮል ሱፔሪየር ጂ ኢኮኖሚ ሁለተኛ ዲግሪነውን በኢኮኖሚክስ ሰራ፡፡ በመቀጠልም ለሁለት
አመታት በዚያው በፖራል በማኔጅመንትና በኢንፎርሜሽን የሥራ ዘርፍ ተሰማርቶ ልምድ አካበተ።
በአውሮፓ/ ትምህርቱን በመከታተል ላይ በነበረበት ጊዜ ከትምህርቱ በተጓዳኝ፣ ሃገሩንና አህጉሩን በተመለከተ
በወቅቱ በነበሩ እንቅስቃሴመ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል። በተለይ፤
1ኛ/ በአውሮፓ የኢት ተማሪዎች ማኅበር የመፅሄት ቦርድ አባል
2ኛ/ በፈረንሳይ የኢት ተማሪዎች ማኅበር ሥራ አ/ኮሚቴ አባል
3ኛ/ በፖሪስ የኢትዮጵያ ተማሪዎች ማኅበር ሥ/አ/ኮማቴ አባል ሆኖ አገልግሏል፡፡
በተጨማሪ፡- በፈረንሳይ የአፍሪካ ተማሪዎች ማኅበር አመራር ውስጥ አባል ሆኖ ወደ ሁዋላ በየአገሮቻቸው
ፖለቲካ ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ ካሳደሩ ወጣት አፍሪካውያን ጋር ጎን ለጎን ሆኖ ሠርቷል።
ታደሠ፣ ከአውሮፓ ቆይታው በጉዋላ ወደ ውድ ሃገሩ ተመልሶ በተለያዩ መንግሥታዊ፣ ዓለም አቀፋዊ እና
መንግሥታዊ ባልሆኑ ድርጅቶች ውስጥ መደበኛ ሠራተኛ በመሆን ለሁለት ዓሠርተ-ዓመታት አገልግሏል።
ከነዚህም መሥሪያ ቤቶች ዋናዎቹ፡-
- የየካቲት 66 የት/ቤት
- የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
- በኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የቴክስታይል ኮርፖሬሽን
- በአ/አ የተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ ኮሚሽን መሥሪያ ቤት ሲሆኑ በተጨማሪ በዝምባቡዌ
አህጉራዊ የሸማቾች መስሪያ ቤት አገልግሏል።
ከኢ-መደበኛ ሥራ ውጭም በትርፍ ጊዜው በበርካታ የማኅበረሰብ ድርጅቶች ውስጥ አስተዋጽኦ አድርጉዋል።
ከነዚህም ዋና ተጠቃሾቹ የሚከተሉት ናቸው-።
- የኢትዮጵያ ቼስ ፎደሬሽን መስራች እና ለረዥም ጊዜ የአመራሩ አባል፤
- የቡል ጨዋታ በኢትዮጵያ እንዲለመድ ሲል የቡል ክለቦች መስራች እና አነቃቂ፤
- የኩላሊት ማጠቢያ መሳሪያ በብዛት ወደ ሃገር በማስገባት ረገድ ከፍተኛ ሚና የተጫወተው የኩላሊት
ሕሙማን መርጃ ማህበር አመራር አባል፤
- የሮተሪ ክለብ ንቁ አባል፤ እና
- ከአዲስ አድማስ መስራቾች እና መሪዎች አንዱ ነበር።

በተጨማሪ፤ ታደሠ አራት መፃሕፍት እና በርካታ መጣጥፍ ደርሶ አሳትሟል። ከነዚህም ውስጥ ሁለቱ
በጤና እና በጤናማ አመጋገብ ላይ ያተኰሩ ጠቃሚ መፃሕፍት ናቸው።
ታደሰ የቤተሰብ ሰው፥ ቁምነገረኛ እና ለወዳጅ ዘመዱ ቀደሞ ደራሽ፥ የዕርዳታ ሥራ ቀስቃሽ እና አደራጅ
የነበረ ሲሆን፤ የዚያኑ ያህል ደግሞ የደስታ እና የጨዋታ ሰው በመሆን በራሱ ጭምር የመቀለድ ተሰጥዎ
ያለው ነበር።
ዛሬ ወንድማችን ታዴን የምንሰናበት ቀን ነው። ሆኖም በመለያዬታችን የምናዝንበት ብቻ ሳይሆን፥ ረዥም
ፍሬያማ ህይወቱን የምንዘክርበትና ለቤተሰቡ መፅናናትን እና መልካሙን የምንመኝበት አጋጣሚ ነው።
ስለሆነም፥ ለመላ ወዳጅ ዘመዱ፤ በተለይም ለባለቤቱ ወ/ሮ አማረች ክፍሌ፥ ለእህቱ ወ/ሮ ምንትዋብ፥
ለልጆቹ ሊድያ፣ መብአ፣ የሺሃረግ፣ ሕሩይ እና እሙዬ፤ እንዲሁም ለሦስቱ የልጅ ልጆቹ ፈጣሪ መፅናናትን
እንዲሰጣቸው እና እንዲጠብቃቸው እንመኛለን።
በመጨረሻ፤ ጊዜ የጣለብን ወረርሽኝ እስከሚወገድ ድረስ ቀናቶችን በጥንቃቄ ለማሳለፍ ስለምንገደድ፤
የስንብቱን ሥርዓቱን በዚሁ ቋጭተን መበተን የኖርብናል። ትናንትና ማታ ላይ ባለቃ ጊዜ ለዛሬ ተዘጋጅቶ
የነበረውን የጠበል ፀዲቅ ሥርዓት በዚህ ህሳቤ እንዲሰረዝ እንደተደረገው፤ ለሃዘነተኛው ቤተሰብ ደህንነት
በማሰብ ሃዘናችንን ለመግለፅም ሆነ ለማፅናናት ወደ ቤተሰቡ መኖሪያ በመሄድ ቆይታ ከማድረግ
እንድንቆጠብ አደራ እንላለን።
ቤተሰቡ፤ በዚህ በመገኘት የሃዘኑ ተካፋይ የሆናችሁትን ሁሉ ከልብ ያመሰግናል።

Text read at the ceremony by Mr.Yeraswork Admassie ( English version )

March 3, 2021

Our dear brother Tadesse Gessesse was born on the 21st of June 1941 from his mother Yeshihareg Yirdaw and his father Gessesse Tedla in Addis Abeba. He lived at his grandmother house in Harar until he was seven years old with his uncle, his sister and other siblings. He led a happy childhood.
Then, he returned to Addis Abeba and finished his primary and secondary school studies in Lycee Guebre Mariam. In 1952, he went to Congo with the Ethiopian peacekeeping troops and participated in peacekeeping missions in the country as a translator.

After returning to Ethiopia and graduating from Lycee Guebre Mariam, he went to France for higher education and received his Master’s degree in Development Economics. As a university student, he was profoundly concerned by Ethiopian and African current affairs, and he was an active member of many Ethiopian and African student associations. He was able to work closely and exchange ideas with other Africans who have achieved great things in their respective countries today. He then worked for 2 years in management and Information technology fields.

In 1967, he returned to Ethiopia and worked in various governmental organizations and private companies for the following 20 years or so, such as the ministry of foreign affairs, Yekatit 66 school, UNDP, UNECA, Consumers International etc...

In his free time, he participated in many community projects as that was one of his greatest ambitions in life. He founded the Ethiopian Chess Federation and was the Chairman for many years. He also built Petanque courts in an effort to encourage elder members of the community to stay active. He played a big role in an Ethiopian association who imported several dialysis machines in order to help those who suffer from kidney failure. He was an active member in the French Rotary and has participated in multiple caritative missions in Ethiopia.He was very generous and always looked for ways to help people and better the community.

In addition, Tadesse has published 4 books in total, of which two were health related, as well as many interesting articles around various subjects. He was passionate about the origin of mankind, space, health, charity, bettering the community and always preached about tolerance and love. He was very reliable and always there for the people he loved. He lived a full life and always made jokes, sometimes even about himself. He had a very positive mindset. He had five children, and three grandchildren.